ኢትዮጵያ የአማኝ ህዝቦች ሀገር ናት፡፡ ሁሉም ዜጋ ሊባል በሚችል ደረጃ ስለራሱ፣ ስለቤተሰቡ፣ ስለሀገሩ እና በቀጣዩ ዓለም ስላለው ዕጣ ፈንታ ወደ ፈጣሪው ይጸልያል፡፡ በየቤተ- ዕምነቱ ያለው ምዕመን ከፈጣሪው ጋር ያለውን ሕብረት ለማጠንከር በጾም፣ በስግደት እና በምጽዋት ይተጋል፡፡ የኃይማኖት አባቶች ቅዱሳን መጻሕፍትን እየገለጡ ለስጋም ለነፍስም የሚበጀውን የፈጣሪን ቃል ያስተምራሉ፡፡ ዝማሬው፣ ሕብረቱ፣ ስብከቱ፣ ተግሳጹ….ሁሉም በቦታው እንዳለ ነው፡፡ እጆች ለጸሎት ለመዘርጋት ሳይሰንፉ፣ ዓይኖች ለምሕረት ለማንባት ሳይደርቁ፣ ጆሮዎች ቃሉን ለማድመጥ ሳይሞሉ፣ እግሮች ለመንበርከክ ሳይዝሉ፤ ትውልዱ ከሥነ-ምግባር እሴቶች ገሸሽ እያለ የመምጣቱ ነገር ለብዙዎች ግራ ነው፡፡ ኢቢሲ ሳይበር የሥነ-ምግባር እና ግብረ-ገብ እሳቤዎችን አስመልክቶ የኃይማኖት መምህራንን አነጋግሯል፡፡
የሚያስተምር አባት፣ የሚሰማ ምዕመን

More Stories
የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል – የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
የ2017 የፈተና አስተዳደር ስረዓት ዉጤታማ ለማድረግ በየደረጃዉ ያሉ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባቸዋል ተባለ።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች ነው።