ኢትዮጵያ የአማኝ ህዝቦች ሀገር ናት፡፡ ሁሉም ዜጋ ሊባል በሚችል ደረጃ ስለራሱ፣ ስለቤተሰቡ፣ ስለሀገሩ እና በቀጣዩ ዓለም ስላለው ዕጣ ፈንታ ወደ ፈጣሪው ይጸልያል፡፡ በየቤተ- ዕምነቱ ያለው ምዕመን ከፈጣሪው ጋር ያለውን ሕብረት ለማጠንከር በጾም፣ በስግደት እና በምጽዋት ይተጋል፡፡ የኃይማኖት አባቶች ቅዱሳን መጻሕፍትን እየገለጡ ለስጋም ለነፍስም የሚበጀውን የፈጣሪን ቃል ያስተምራሉ፡፡ ዝማሬው፣ ሕብረቱ፣ ስብከቱ፣ ተግሳጹ….ሁሉም በቦታው እንዳለ ነው፡፡ እጆች ለጸሎት ለመዘርጋት ሳይሰንፉ፣ ዓይኖች ለምሕረት ለማንባት ሳይደርቁ፣ ጆሮዎች ቃሉን ለማድመጥ ሳይሞሉ፣ እግሮች ለመንበርከክ ሳይዝሉ፤ ትውልዱ ከሥነ-ምግባር እሴቶች ገሸሽ እያለ የመምጣቱ ነገር ለብዙዎች ግራ ነው፡፡ ኢቢሲ ሳይበር የሥነ-ምግባር እና ግብረ-ገብ እሳቤዎችን አስመልክቶ የኃይማኖት መምህራንን አነጋግሯል፡፡
የሚያስተምር አባት፣ የሚሰማ ምዕመን
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።