የገንዘብ ሚኒስቴር ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ዕቃዎችን ወደ ሀገር ማስገባትን በተመለከተ ለጉምሩክ ኮሚሽንና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ሰርኩላር አስተላልፏል።በዚህም ወደ ሀገር እንዳይገቡ በሕግ ክልከላ ከተደረገባቸው የነዳጅ አውቶሞቢሎች እና የፀጥታና ደህንነት ዕቃዎች ውጪ ሌሎች ዕቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ወደ ሀገር እንዲገቡ በመንግሥት የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ ይኸው ተግባራዊ እንዲደረግ አሳስቧል።መንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ ባደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ፤ የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያው አማካኝነት እንዲወሰን ማድረጉ እና ይኸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል።
EBC
More Stories
ቻይና ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ53 ከአፍሪካ ሀገራት የተመረተ የቡና ምርት ወደ ገበያዋ እንዲገቡ ክፍት አደረገች
ዓመታዊ የወጪ ንግድ ያስገኘው ገቢ ጨምሯል ተባለ
አዲሱ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር