በ2016 የትምህርት ዘመን ክልላዊ 8ኛ ክፍል ፈተና ከተፈኑ ተማሪዎች 42.93 ከመቶ ተማሪዎች ከ50 % በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ እንዳስታወቁት በክልሉ በ2016 የትምህርት ዘመን 42.93 ከመቶ ተማሪዎች ከ50% በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል ።በክልሉ በ2016 ዓ.ም 21 ሺህ 428 ወንዶች እና 23 ሺህ 658 ሴቶች በድምሩ 45 ሺህ 86 ተማሪዎች ፈተና ላይ መቀመጣቸውን አቶ አልማው ገልፀዋል ።ክልል አቀፍ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ከተፈተኑት 45 ሺህ 86 ተማሪዎች መካከል ወንድ 9 ሺህ 836 ሴት 9 ሺህ 519 በድምሩ 19 ሺህ 355 ተማሪዎች ከ50 % በላይ ውጤት አቶ አልማው ተናግረዋል።እንደ ኃላፊዉ ገለጻ በፈተናዉም ከ ዳዉሮ ዞን ኤምቲ የአንደኛና መካካለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ተስፋለም ታምራት አማካይ ነጥብ 94.17 ፐርሰንታይል 100 እና አጠቃላይ ዉጤት 659 በማምጣት ከፍተኛ ዉጤት ሆኖ ተመዝግቧል ብለዋል።በ2016 የትምህርት ዘመን ከትምህርት ቤት እስከ ክልል ኩረጃን ለማስቀረት በተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ተማሪዎች የራሳቸውን ውጤት በጥረት ማምጣታቸዉን ተናግረዉ ለዚህም ስኬት ተባባሪ ለሆኑት አካላት በክልሉ ትምህርት ቢሮ ስም አቶ አልማው ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።ተማሪዎች በgoogle account sw.ministry ብለው በመግባት view result የሚለውን በመጫን መመዝገቢያ ቁጥራቸውንና ስማቸውን በማስገባት ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማወቅ እንደሚችሉ የቢሮ ኃላፊዉ አስታውቀዋል ። የዘገበው የክልሉ መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው ።
ክልላዊ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የፈተና ዉጤት ይፋ ሆነ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች