እ.ኤ.አ. ኦገስት 16 ቀን 2024 ዓ.ም. ጠዋት ከህንድ ሙምባይ ወደ አዲስ አበባ ለመብረር በዝግጅት ላይ ወደነበረ አውሮፕላን የሚጫኑ ሻንጣዎችን ይዞ ወደ አውሮፕላኑ በመጎተት ላይ በነበረ ጋሪ ላይ ከተጫኑ ሻንጣዎች በአንዱ እሳት መታየቱን አየር መንገዱ አስታውቋል። ክስተቱ ጋሪው ከራምፕ አካባቢ ወደ አውሮፕላኑ በመሄድ ላይ ሳለ እንደተከሰተም ነው የተገለፀው።ይህንንም ክስተት የተመለከቱ በሙምባይ ያሉ የደህንነት ፣ የጸጥታ እና የእሳት አደጋ ባለሞያዎች እሳት የያዘውን ሻንጣ በመለየት እሳቱን በቁጥጥር ስር አውለዋል። አውሮፕላኑ አስፈላጊው ተጨማሪ የደህንነት ፍተሻ ከተደረገለት በኋላ እና አስጊ ነገር አለመኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ በረራውን አካሂዷል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሙምባይ ኤርፖርት ባለስልጣናትና የሚመለከታቸው አካላት የክስተቱን ምንጭ በመመርመር ላይ በመሆናቸው ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰው እንደሚያስታውቅ ገልጿል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።