የአዲስ ቱሞሮ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የማስጀመሪያ መርሐ- ግብር ተካሂዷል፡፡በ35 ሄክታር መሬት ላይ ከቻይናው “ሲሲሲሲ” ጋር በመተባበር የሚገነባው ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በከተማ ውስጥ አዲስ ከተማን የመገንባት ያህል ግዙፍ ፕሮጀክትመሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡የኢኮኖሚ ዞኑ በውስጡ ትላልቅ ሞሎችን፣ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን፣ ቢሮዎችን፣ የትምህርት እና የጤና ተቋማትን እንዲሁም ሰፋፊ መዝናኛዎችንና የውሃ አካላትን እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ማዕከላትን ያካተተ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡አዲሱ የኢኮኖሚ ዞን ለመዲናዋ አዲስ ገፅታ የሚያላብስ፣ ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነቷን የሚያጎላ፣ ተጨማሪ የውበት ምንጭ የሚሆን፣ ለነዋሪዎች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር እና ንግድን የሚያሳልጥ ትልቅ ዓለም አቀፍ የግብይት ማዕከል ይሆናል ብለዋል፡፡በተጨማሪም ኢኮኖሚ ዞኑ ማህበራዊ አገልግሎቶችን የሚሰጡ መሰረተ ልማቶችን ያካተተ ሲሆን ፥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቆ ወደ ስራ እንደሚገባ ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች