በሀረሪ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በይፋ ተጀምሯል።
ክልላዊ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት የሚቆይ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ተገኘወርቅ ጌጡ የምክክር ሂደቱ ለኢትዮጵያ ተስፋን በማለምለም ችግሮችን ከግጭት ይልቅ በውይይት የመፍታት ባህል የሚጎለብትበት እንደሆነ ገልፀዋል።
በመድረኩ የተለያዩ የማህበረሰብ ወኪሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሶስቱ የመንግሥት አካላት ወኪሎች፣ የተለያዩ ማህበራት እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።
በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረኩ ክልላዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ሀሳቦችና አጀንዳዎች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
EBC
More Stories
በቴፒ ከተማ ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የመሶብ አንድ ማዕከል ከእንግልትና ከምልልስ እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ