መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያን ከመጠበቅ ባሻገር ለሀገሪቱ ስፖርት ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ ተናግረዋል፡፡ መቻል የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያስጠሩ ድንቅ ስፖርተኞች መፍለቂያ መሆኑንም ሌተናል ጀነራሉ ገልጸዋል፡፡ መነሻውን እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው “መቻል ለኢትዮጵያ” የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል። “ስፖርት ጤናማ እና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር ወሳኝ ነው” ያሉት የጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪ እና የተኩስ አመራር ሃላፊ ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ፤ በኦሎምፒክ የመጀመሪያ ወርቅ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ያስገኘው ሻምበል አበበ ቢቂላ የመቻል ስፖርት ክለብ ትሩፋት እንደሆነ ጠቀሰዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የስፖርት ውድድር መድረኮች ለተቀዳጀቻቸው ድሎችም መቻል ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ እንዳበረከተ አስታውሰዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ ባሻገር የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ ያደረጉ ብርቅዬ አትሌቶችን እና እግር ኳስ ተጫዋቾችን ያፈራ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። የመቻል 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ::
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።