መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያን ከመጠበቅ ባሻገር ለሀገሪቱ ስፖርት ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ ተናግረዋል፡፡ መቻል የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያስጠሩ ድንቅ ስፖርተኞች መፍለቂያ መሆኑንም ሌተናል ጀነራሉ ገልጸዋል፡፡ መነሻውን እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው “መቻል ለኢትዮጵያ” የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል። “ስፖርት ጤናማ እና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር ወሳኝ ነው” ያሉት የጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪ እና የተኩስ አመራር ሃላፊ ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ፤ በኦሎምፒክ የመጀመሪያ ወርቅ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ያስገኘው ሻምበል አበበ ቢቂላ የመቻል ስፖርት ክለብ ትሩፋት እንደሆነ ጠቀሰዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የስፖርት ውድድር መድረኮች ለተቀዳጀቻቸው ድሎችም መቻል ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ እንዳበረከተ አስታውሰዋል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ ባሻገር የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ ያደረጉ ብርቅዬ አትሌቶችን እና እግር ኳስ ተጫዋቾችን ያፈራ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። የመቻል 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ::
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች