የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ስዊስ ዲያግኖስቲክስ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል፡፡ የህክምና ማዕከሉ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ራዕይ ለማሳካት እንደሚያግዝ ከንቲባዋ ገልጸዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት እንዲስፋፋ እና ሌሎች የግል ባለሃብቶች በጤናው ዘርፍ ይበልጥ እንዲሰማሩ የከተማ አስተዳደሩ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡ መሰል የጤና ማዕከላት መበራከት ከሃገር ወጥተው መታከም የማይችሉ ወገኖች የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ከማስቻሉም ባሻገር የውጪ ምንዛሬን እንደሚያስቀር ከንቲባዋ በማኀበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።