የኢትዮጵያ ቆይታችን አስደሳች እና ሀገሪቱም በፈጣን ለውጥ ላይ መሆኗን የተገነዘብንበት ነው ሲሉ የናይጀሪያ የቀድሞ ታላላቅ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ተናገሩ፡፡የቀድሞው የናይጀሪያ የእግር ኳስ ኮከብ ንዋንኩ ካኑን ጨምሮ የቀድሞ የአህጉሪቱ ታላላቅ ተጫዋቾች በአዲስ አበባ ሸነን አፍሪካ ፌስቲቫል ለመታደም አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል፡፡በቆይታቸውም ከፌስቲቫሉ በተጨማሪ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ዛሬ ማለዳ ደግሞ በወዳጅነት ፓርክ በመገኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደረጉ ሲሆን፤ በስፍራው ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ የቀድሞው የናይጀሪያ እግር ኳስ ኮከብ ንዋንኩ ካኑ በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ እጅግ ውብና የሚያስደንቅ ባህል ያላት ሀገር መሆኗን ተናግሯል፡፡በኢትዮጵያ ቆይታችን የተደረገልን አቀባበልና እንክብካቤ ቤታችን ያለን ያህል እንዲሰማን አድርጓል ያለው የናይጀሪያ የቀድሞ እግር ኳስ ኮከብ፤ በቀጣይም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ እንደሚመጣ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡በቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ራዕይ መሰረት አድርገው እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ስራዎችን ስለመጎብኘታቸውም ተናግሯል፡፡ሌላኛው የናይጀሪያ የቀድሞ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ታሪቦ ዌስት፤ በቆይታቸው የተለያዩ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸውን መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።