የኢትዮጵያ ቆይታችን አስደሳች እና ሀገሪቱም በፈጣን ለውጥ ላይ መሆኗን የተገነዘብንበት ነው ሲሉ የናይጀሪያ የቀድሞ ታላላቅ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ተናገሩ፡፡የቀድሞው የናይጀሪያ የእግር ኳስ ኮከብ ንዋንኩ ካኑን ጨምሮ የቀድሞ የአህጉሪቱ ታላላቅ ተጫዋቾች በአዲስ አበባ ሸነን አፍሪካ ፌስቲቫል ለመታደም አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል፡፡በቆይታቸውም ከፌስቲቫሉ በተጨማሪ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ዛሬ ማለዳ ደግሞ በወዳጅነት ፓርክ በመገኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደረጉ ሲሆን፤ በስፍራው ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ የቀድሞው የናይጀሪያ እግር ኳስ ኮከብ ንዋንኩ ካኑ በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ እጅግ ውብና የሚያስደንቅ ባህል ያላት ሀገር መሆኗን ተናግሯል፡፡በኢትዮጵያ ቆይታችን የተደረገልን አቀባበልና እንክብካቤ ቤታችን ያለን ያህል እንዲሰማን አድርጓል ያለው የናይጀሪያ የቀድሞ እግር ኳስ ኮከብ፤ በቀጣይም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ እንደሚመጣ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡በቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ራዕይ መሰረት አድርገው እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ስራዎችን ስለመጎብኘታቸውም ተናግሯል፡፡ሌላኛው የናይጀሪያ የቀድሞ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ታሪቦ ዌስት፤ በቆይታቸው የተለያዩ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸውን መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።