የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በጣሊያን ሴኔት የውጭ ጉዳይና መከላከያ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ሴናተር ስቴፋኒያ ክራክሲ የተመራ የጣሊያን የፓርላማ ልዑክን ተቀብለው አነጋግረዋል።በውይይታቸውም፤ የሁለትዮሽ፣ አህጉራዊ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ መክረዋል።በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ ያሉ የተለያዩ የልማት እና የጸጥታ ችግሮችን በተመለከተም ሁለቱ ወገኖች ተወያይተዋል።የጣሊያን መንግስት ኢትዮጵያን በተለያዩ ዘርፎች ለመደገፍ የሚያደርገውን ትብብር አምባሳደር ታዬ አድንቀዋል።በሀገራቱ መካከል ያለው ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ሁለቱ ወገኖች ጠቁመዋል።አምባሳደር ታዬ ከሰብዓዊ ዕርዳታ በተጨማሪ በቀጠናው በልማት ፕሮጀክቶች ላይ በትብብር መስራት ለበርካታ ዜጎች ህይወት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አንስተዋል።በተጨማሪም ቀጠናዊ የጸጥታ ችግሮችን ከመቅረፍ አኳያ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ትብብር እና መግባባት አስፈላጊነት ላይ ምክክር መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።