በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ለእግር ጉዞ ወጥቶ ከሳምንት በላይ በተራራማ ስፍራዎች ጠፍቶ የቆየው ግለሰብ ብዙ ውሃ እየጠጣ ህይወቱን ማቆየቱ ተሰምቷል።
ሉካስ ማክሊሽ የተባለው ይህ ግለሰብ በተራራማ ስፍራ ለእግር ጉዞ (ሃይኪንግ) በወጣበት በመጥፋት ለ10 ቀናት ብቻውን አሳልፎ ቤተሰቦቹ ሲያፈላልጉት ቆይተዋል።
በወቅቱ በአካባቢው በተከሰተ ሰደድ እሳት ምክንያት በስፍራው የነበሩ አቅጣጫ ጠቋሚዎች መውደማቸው ግለሰቡ እንደ አወጣጡ እንዳይመለስ አድርጎታል።
እንደወጣ የቀረውን ቤተሰባቸውን አፋልጉን ያሉት ቤተሰቦቹም ለፖሊስ ጥቆማ ሰጥተው፥ በአነስተኛ ሰው አልባ አውሮፕላን በተደረገ ፍለጋ በህይወት መገኘቱ ተሰምቷል።
በወቅቱ ግለሰቡ በተራራማው ስፍራ የድረሱልኝ ጥሪ ያቀርብ የነበረ ቢሆንም፥ በትክክል አቅጣጫው ባለመታወቁ ምክንያት ለቀናት ብቻውን እንዲቆይ አስገድዶት እንደነበርም ነው የተገለጸው።
በተራራማው ስፍራው ቆይታው ታዲያ በሚረግጠው ጫማ ውሃ በማጠራቀም እስከ 4 ሊትር ውሃ በቀን ይጠጣ እንደነበር ተናግሯል።
በወቅቱ ሲገኝ ሰውነቱ ተጎሳቁሎና ከስቶ ቢታይም ለህይወቱ አስጊ አይደለም ተብሏል።
Ahadu Radio
More Stories
የአሜሪካ ወታደሮች ላይ የተሰነዘረውን የጥቃት ሙከራ ተከትሎ ዋሽንግተን ኢራን ላይ “ከፍተኛ” ጥቃት ፈጸመች
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ከ37 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ተገለፀ::
አሜሪካ የመርከቦችን እንቅስቃሴ እያወኩ ነው ባለቻቸው የኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ አዲስ ጥቃት ፈጸመች፡፡