የኢፌዴሪ መከላከያ ጀኔራል መኮንኖች አዲስ አበባ ከሚኖሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ጋር በዛሬው ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የአማራ ክልል የሰላም ኮንፈረንሰ ውይይት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተደርጓል፡፡
ወይይቱን የመሩት የክልሉ ተወላጅ የሆኑት የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ ÷ የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም ናቸው።
ተሳታፊዎችም አለ የሚሉትን ችግር በነፃነት በጥያቄም በሃሳብም የገለፁ ሲሆን ÷ ጥያቄያቸው ለክልል መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ተደራጅቶ እንደሚቀርብ ተገልጿል።
በጉባኤው ማጠቃለያው የመድረኩ ተሳታፊዎች ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫም አውጥተዋል መባሉን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች