ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ከጥቅምት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ መቆየቱ ይታወቃል።ጽ/ቤቱ ሰኔ 11፣ 2016 ዓ.ም ዳግም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፤ በጊዜያዊነት የጀመራቸው አገልግሎቶች ፓስፖርት ማደስ፣ የጠፋ ፓስፖርት መተካት እና የተበላሸ ፓስፖርት እርማት መስጠት ናቸው።በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ፓስፖርታቸውን ሲያሳድሱ የነበሩ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች የቅርንጫፉ አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት አዲስ አበባ ድረስ ለመሄድ ይገደዱ እንደነበር ገልጸዋል።በዚህም ለአላስፈላጊ እንግልት ተዳርገው እንደነበር ጠቅሰው ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዳግም ስራ በመጀመሩ መደሰታቸውን መግለጻቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …