በጀርመን አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ 2ኛ መርሐ ግብር ዛሬ ተጀምሯል። በምድብ 1 አዘጋጇ አገር ጀርመን ከሀንጋሪ ጋር ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ በስቱትጋርት አሬና ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ በጀርመን 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።ለጀርመን የማሸነፊያ ግቦቹን ሙሲያላ በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጉንዶጋን ከረፍት መልስ ከመረብ አሳርፈዋል።ጀርመን በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ ስኮትላንድን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፏ ይታወሳል።እናም የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ጀርመን ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቷን ያረጋገጠች የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች።ጀርመን የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋን እሁድ ከስዊዘርላንድ ጋር የምታደርግ ሲሆን፤ ሀንጋሪ በበኩሏ ከስኮትላንድ ጋር ትጫወታለች።
EBC
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ