በዘንድሮው ሀገር አቀፍ የክረምት ወቅት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 50 ሚሊየን ወገኖች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላከተ፡፡የአገልግሎቱ ንቅናቄ የፊታችን ረቡዕ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በይፋ እንደሚጀመር የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የሰላም ሚኒስቴር እና ትምህርት ሚኒስቴር በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ከ39 ሚሊየን በላይ በጎ ፈቃደኞች በሚሳተፉበት በዚህ መርሐ-ግብርም 50 ሚሊየን ወገኖች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላክቷል፡፡ኢትዮጵያዊ አብሮነትን እንደሚያጠናክር የተገለጸው ይህ ንቅናቄ በሦስቱ ተቋማት ቅንጅት በየደረጃው ይወርዳል ተብሏል፡፡“በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ በሚካሄደው በዚህ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 14 የስምሪት ዘርፎች መኖራቸውም ተብራርቷል፡፡የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለትምህርት ተደራሽነት የሚያበረክተውን የጎላ ሚና በመገንዘብ 20 ሺህ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ እንደሚሳተፉም ነው የተገለጸው፡፡
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 50 ሚሊየን ወገኖች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገለጸ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች