ሰኔ 16 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 40ኛው የሻንበል አበበ ቢቂላ ማራቶን ውድድር ወደ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም መራዘሙን አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
በተመሳሳይ ከሰኔ 11 እስከ 15 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 12ኛው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሰኔ 25 እስከ 29 ቀን እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
ውድድሮቹ የሚካሄዱት በሐዋሳ ከተማ መሆኑን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡
ፌደሬሽኑ ለሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አሥተዳደሮች፣ ክለቦች፣ ተቋማት እና የግል ተወዳዳሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት÷ ምዝገባው እስከ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን አስታውቋል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።