የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ቢስት ባር” በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “ቢስት ባር” የተለያዩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የብሔረሰቡ ተወላጆችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በሚዛን አማን ከተማ መከበር ጀምሯል።”ቢስት ባር” የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል ሲሆን ህዝቡ በሰላምና ጤና ወደ አዲስ ዘመን በመሻገሩ እና ከተለያዩ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ተጠብቀው ለአዲስ ቀን በመድረሳቸው ለፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡በብሔሩ አባላት ዘንድ በዓሉ ሲመጣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የይቅርታና የአብሮነት መንፈስ የተሞላበት ልዩ ዕለት በመሆኑ በድምቀት ያከብሩታል።በዓሉ በትላንትናው ዕለት የብሔሩ መነሻ ቦታ መሆኑን በሚነገርለት በሼይ ቤንች ወረዳ በምትገኘው ዣዥ ቀበሌ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችና የጎሳ መሪዎች በተገኙበት የተከበረ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የበዓሉ ማጠቃለያ ዝግጅት በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ስርአቶች በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ባማረ ሁኔታ በመከበር ላይ ነው። ለበዓሉ ድምቀት የሚሆን የፖሊስ ማርቺንግ ባንድ የጎዳና ላይ ትርኢቱን አቅርቧል።ዘጋቢ ጦያር ይማም ከሚዛን ጣቢያችን
ደሬቴድ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች