ካርሎ አንቸሎቲ አምስት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ያነሱ አሰልጣኝ በመሆን አዲስ ታሪክ አጽፈዋልሪያል ማድሪድ የጀርመኑን ቦርሺያ ዶርትሙንድ በማሸነፍ 15ኛ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫውን አነሳ።ማድሪድ በምሽቱ የዌምብሌይ የፍጻሜ ጨዋታ ዳኒ ካርቫሃል በ74ኛው፤ ቪንሺየስ ጁኒየር በ83ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ነው ለድል የበቃው።የኤዲን ቴርዚች ቡድን በመጀመሪያው አጋማሽ የፈጠራቸውን የጎል እድሎች መጠቀም አለመቻሉ ዋጋ አስከፍሎታል።በተለይ ካሪም አድየሚ ሁለት የጎል እድሎችን ያመከነበት አጋጣሚ በድጋፍ ድምጻቸው ዌምብሌይን ላደመቁት የዶርትሙንድ ደግፊዎች የሚያስቆጩ ነበሩ።
Al-Ain
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ