ከከተማ እስከ ወረዳ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮችን ያሳተፈ የ2016 አፈጻጸም ግምገማ እና የ2017 ዕቅድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መድረኩን ሲያስጀምሩ እንደገለጹት፥ በአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመዘገብ ካስቻሉ በርካታ ጉዳዮች መካከል ገቢ ከማሳደግ አንጻር የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት ወሳኝ ሚና አላቸው።
ገቢ ለአንድ ሀገር ብልፅግና የጀርባ አጥንት ነው ያሉት ከንቲባዋ፣ በበጀት ዓመቱ 146.84 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን ጠቅሰው፣ ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ44.16 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች በ2017 አዲስ አበባ ከምታመነጨው ኢኮኖሚ በተገቢው መጠን ገቢ በማሰባሰብ የተጀመረውን ሁለንተናዊ ለውጥ ማሳለጥ እንደሚገባ ማሳሰባቸውን ከአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች