በሀረሪ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በይፋ ተጀምሯል።
ክልላዊ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት የሚቆይ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ተገኘወርቅ ጌጡ የምክክር ሂደቱ ለኢትዮጵያ ተስፋን በማለምለም ችግሮችን ከግጭት ይልቅ በውይይት የመፍታት ባህል የሚጎለብትበት እንደሆነ ገልፀዋል።
በመድረኩ የተለያዩ የማህበረሰብ ወኪሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሶስቱ የመንግሥት አካላት ወኪሎች፣ የተለያዩ ማህበራት እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።
በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረኩ ክልላዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ሀሳቦችና አጀንዳዎች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች