የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ሚና የሚያሳድግ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ አስገነዘቡ፡፡የ2016 በጀት ዓመት የግብር አሰባሰብ ዕቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡በመድረኩ አቶ አህመድ ሽዴ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ለግብር ከፋዮች በሰጡት ማብራሪያ፤ መንግስት እየሰበሰበ ያለው ገቢ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ ነው ብለዋል።የኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ሚና የሚያሳድግ ነው ሲሉም ነው የገለጹት፡፡ማሻሻያው ለሀገር ውስጥ አምራቾች ቅድሚያ ይሰጣል በማለት ገልጸው÷ በብድር ረገድ በተለይ መንግስት ከዚህ በፊት በስፋት ይወስደው የነበረውን ብድር በማስቀረት የተሻለ የብድር ፍሰት ለግሉ ዘርፍ እንደሚኖር አንስተዋል፡፡መንግስት የገቢ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን ስራ ግብረ ሃይል በማቋቋም ጭምር በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ነውም ብለዋል፡፡በበጀት ዓመቱ ዕቅድ አስቀድሞ ከተቀመጠው በተጨማሪ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት አንድ በመቶ ተጨማሪ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ በበኩላቸው÷ ባለፉት አምስት ዓመታት ገቢ በሶስት እጥፍ ማደጉን ገልጸዋል፡፡በዚህም በ2016 በጀት ዓመት 513 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን ገልጸው÷ ይህም የዕቅዱን 96 በመቶ መሆኑን አንስተዋል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች