የገቢዎች ሚኒስቴር ከመካከለኛ ግብር ከፋዮች ጋር በታክስ ህግ ተገዥነት እና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ፤ የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ከግብር የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል። የገቢ አሰባሰቡ ህግና ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን ለማስቻል በመንግስት የሚመራ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ ተቋማት በጋራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል። የገቢዎች ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በበኩላቸው፤ የገቢ አሰባሰቡን ለማሳደግ በቀጣይ ዓመታት 5 ዋና ዋና ስትራቴጂክ እቅዶች ተነድፈው እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ገቢን ማሳደግ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች