የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከጣሊያን አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በቱሪዝም ዘርፍ በጣሊያን መንግሥት ትብብር ስለሚከናወኑ ተግባራት ተነጋግረዋል።
አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ፥ የጣሊያን መንግሥት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሚያከናውናቸው የቅርስ እድሳት እና የቱሪዝም ልማት ስራዎች የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም በቱሪዝም ዘርፍ የሰው ኃይል ልማት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት መደረሱን ከቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች