የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከጣሊያን አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በቱሪዝም ዘርፍ በጣሊያን መንግሥት ትብብር ስለሚከናወኑ ተግባራት ተነጋግረዋል።
አምባሳደር ኦገስቲኖ ፔልሲ፥ የጣሊያን መንግሥት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሚያከናውናቸው የቅርስ እድሳት እና የቱሪዝም ልማት ስራዎች የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም በቱሪዝም ዘርፍ የሰው ኃይል ልማት ላይ በትብብር ለመስራት ከስምምነት መደረሱን ከቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ