July 15, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር በሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋዜማ፣ የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ ከሆኑት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል።

በመጪው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ለመወያየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ተግባራት ጥበብ ለመቅሰም የተቻለ ሲሆን፤ በተለይም የቢያፍራን የሰላም ሂደት በመምራት ያካበቱትን ልምድ ማጋራታቸውን አመልክተዋል።

ይህም ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ኦባሳንጆ ለሚያበረክቱት በዋጋ የማይተመን አስተዋጽኦ ሁልጊዜም የላቀ ምስጋናዋን ታቀርባለች ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።

ኢዜአ