የኮሚሽኑ ቃል-አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፣ መሰረታዊ ችግሮችን በሀገራዊ ምክክር መፍታት ለሀገሪቱ አዲስ ምዕራፍ ነው። ሀገራዊ ምክክር ብዙ ሂደቶችን አልፎ የምክክር መድረክ መፈጠሩ ለዚች ሀገር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ መምከር ከጀመረች አራት ዓመታትና ጥቂት ወራት መቆጠሩን አስታውሰው፤ ኮሚሽኑ ከተቋቋመ ጀምሮ ኢትዮጵያ በምክክር ሂደት ላይ መሆኗንና ወደፊትም እየመከረች መቀጠል እንዳለባት ገልጸዋል፡፡
ሐምሌ 8 የሚጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያውያን እጅግ መሠረታዊና ሀገራዊ በሆኑ አጀንዳዎች ላይ ተመካክረው መግባባት ላይ የሚደርሱበት ይሆናል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እየተዋጋች፣ እየተጋጨች፣ ነገሮች እየተወሳሰቡ መቀጠል እንደሌለባት በመግለጽ፤ ልዩነቶችና አለመግባባት ዛሬም አለ፣ ወደፊትም ይኖራል። ችግሮች የሚፈቱበት መንገድ ግን በምክክርና ሰለጠነ ዕሳቤ መሆን አለበት ብለዋል።
በመሣሪያ ሰው እያለቀ፣ ንብረት እየወደመ፣ ሀገር ወደኋላ እየተመለሰና ማኅበራዊ ግንኙነቶች እየሻከሩ መቀጠል እንደሌለበት ጠቅሰው፤ ሀገራዊ ምክክሩ ችግሮች የሚፈቱበት መሣሪያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጋዜጣ_ፕላስ
More Stories
አፍሪካ በጸጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት የምታነሳው ጥያቄ ፍትሃዊ ነው – የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በመከላከያ ጠቅላይ መመሪያ ግቢ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በይፋ አሥጀምረዋል።
የክልሉ ወጪዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችል የገቢ አሰባሰብ አቅም እየተፈጠረ ነው፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)