April 28, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

700 ሱቆችን በአንድ ጣራ ስር የያዘው የዓለማችን ግዙፉ የገበያ ማዕከል

ግዝፈቱና ውበቱ ብዙዎችን ያስደመመው የደቡብ ኮሪያው ሺንሴጌ ሴንተም ሲቲ በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ የዓለማችን ግዙፉ የገበያ ማዕከል ሆኖ ተመዝግቧል።

በደቡብ ኮሪያ “ቡሳን” ከተማ የሚገኘው ይህ አስደናቂ የሕንፃ ጥበብ ውጤት ለገበያ ብቻ ሳይሆን ለመዝናኛም ተመራጭ ስፍራ ሆኗል።

ማዕከሉ በ16 ፎቆች ላይ ያረፉ 700 የሚጠጉ ሱቆችን የያዘ ሲሆን ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ ታዋቂ ብራንዶችን በአንድ ጣራ ስር ያገናኛል።

በውስጡም የበረዶ ላይ መንሸራተቻ፣ የጎልፍ መለማመጃ፣ ስፓ፣ ዘመናዊ ሲኒማ ቤቶችና ግዙፍ የምግብ አዳራሾችን አካቷል።

ይህ የገበያ ማዕከል በቀን በአማካይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝዎችን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለደቡብ ኮሪያ የቱሪዝም ዘርፍም ከፍተኛ ገቢ እያስገኘ እንደሚገኝ ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።