የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች የተዘጋጀውን የነፃ የአየር ሰዓት ድልድል ይፋ አድርጓል።
የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ምርጫውን በጊዜ ሰሌዳው መሠረት ለማካሄድ ቦርዱ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የግል ዕጩዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ሕጉን ተከተለውና በኃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በመድረኩ ላይ የምርጫ የሕግ ማዕቀፎችን፣ የኦፕሬሽን ሥራዎችን እና የቅስቀሳ ሥነ-ምግባርን በተመለከተ በቦርዱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የሕግ ባለሙያዎች ዝርዝር ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የወጣው የነፃ የአየር ሰዓት ድልድል ለወንድ የግል ዕጩዎች እያንዳንዳቸው በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ እና በጋዜጣ የ15 ደቂቃ ዕድል ይሰጣል።
ሴት እና አካል ጉዳተኛ ዕጩዎችን ለማበረታታት ደግሞ ቦርዱ ልዩ ድልድል አድርጓል። በዚህም መሠረት ሴት ዕጩዎች አንድ ተጨማሪ ዕድል፣ ወንድ አካል ጉዳተኞች አንድ ተጨማሪ ዕድል፣ እንዲሁም ሴት አካል ጉዳተኛ ዕጩዎች እስከ አምስት የሚደርስ ተጨማሪ የአየር ሰዓት ዕድል እንዲያገኙ ተወስኗል።
በመጨረሻም ተሳታፊዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች በቦርዱ አመራር አባላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
More Stories
ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን ዳግም ዘጋች
የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት ዳግም ያረጋገጡ አዲስ የአርኪዮሎጂ ግኝቶች…
በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የበልግ ተጠቃሚ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ዝናብ ያገኛሉ ተባለ