
የአሜሪካ አየር ሀይል በሶሪያ ቁልፍ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል የተገደለው ሰው በመጨረሻም ዶሮ አርቢ ሆኖ መገኘቱን አረጋግጫለሁ ብላለች
የአሜሪካ አየር ሀይል በሶሪያ ቁልፍ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል የተገደለው ሰው በመጨረሻም ዶሮ አርቢ ሆኖ መገኘቱን አረጋግጫለሁ ብላለች
የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል በስህተት በአሜሪካ ጦር የተገደለው ሰው የ60 ዓመት ሶሪያዊ አርሶ አደር ነበር
አሜሪካ የአልቃይዳ መሪ ነው በሚል ገድየዋለሁ ያለችው ድሃ ገበሬ ሆኖ ተገኘ፡፡
የአሜሪካ አየር ሀይል ጦር በሶሪያ የሚንቀሳቀሰው አልቃይዳ ቁልፍ አመራር ነው በሚል ነበር የድሮን ጥቃት የፈጸመው፡፡
ጥቃቱም ውጤታማ እንደነበር እና የአልቃይዳ አመራር መገደሉንም ሀገሪቱ አስታውቆም ነበር፡፡
ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ እንደተፈጸመ የተገለጸው ይህ ጥቃት ኢላማውን እንደሳተ እና በዶሮ እርባታ የሚተዳደር አርሶ አደር ስለመገደሉ በወቅቱ የሟች ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡
ይህ ጥቆማ የደረሰው የአሜሪካ አማዕከላዊ እዝም ባደረገው ማጣራት በወቅቱ በተፈጸመው ጥቃት የተባለው የአልቃይዳ መሪ ሳይሆን ሉፍቲ ሀሰን ማስቶ የተሰኘ ዶሮ አርቢ አርሶ አደር እንደተገደለ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ይፋ ባደረገው ምርመራ የ60 ዓመቱ አዛውንት በተፈጸመው የድሮን ጥቃት እንደተገደለ ይህም ስህተት መሆኑን አረጋግጠናልም ብሏል፡፡
በአሜሪካ የሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን ጥቃት በስህተት የተገደለው ማስቶ ወንድም በበኩሉ ወንድሙ ዶሮ ከማርባት እና በግ ከመንዳት ውጪ ከአልቃይዳም ሆነ ከየትኛውም ቡድን ጋር ግንኙነት የሌለው ሰው ነው ብሏል፡፡
Al-Ain
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ