March 15, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አርሰናል ኤቨርተንን በማሸነፍ ከሲቲ ያለውን ልዩነት ወደ 10 አስፍቷል

በ30ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚር ሊግ አርሰናል ኤቨርተንን 2 ለ 0 በማሸነፍ ይበልጥ ወደ ዋንጫው ቀርቧል፡፡

በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ተቀይረው የገቡት ቪክቶር ዮኬሬስ 89ኛው ደቂቃ ላይ እና ወጣቱ ማክሰ ዶውማን በባከነ ሰዓት የመድፈኞቹን ዋሳኝ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

የ16 ዓመቱ እንግሊዛዊ ባለተሰጥኦ ወጣት ዶውማን በፕሪሚየር ሊጉ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ሆኗል፡፡ ዶውማን ሜዳ ውስጥ በቆየበት 16 ደቂቃ ብቻ አንድ ግብ ከማስቆጠሩ በተጨማሪ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

መድፈኞቹ ሊጉን በ70 ነጥብ ሲመሩ ማንችስተር ሲቲ በ60 ነጥብ ይከተላል፡፡