February 27, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ዕድገት ማነቆ የሚሆኑ ችግሮች ተለይተው በዘላቂነት መፈታት አለባቸው፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ማሻ፤ የካቲት 20/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከባለሃብቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ክልላዊ የኢንቨስትመንት ፎረም በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።

‎መድረኩ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በተደራጀ መንገድ ለመፍታትና የክልሉን የኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።

‎የፎረሙን ማጠቃለያ መድረክ የመሩት የክልሉ ርዕሰመስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ያደጉ ሀገራት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ያስመዘገቡት በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ታግዘው መሆኑን ተናግረዋል።

‎የኢንቨስትመንት መሠረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት በትብብር መስራት እንደሚገባ የገለጹት ርዕሰመስተዳድሩ ከአገልግሎት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የማያዳግም እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ተናግረዋል።

‎የግሉ ዘርፍ የፈጠረውን አቅም በመጠቀም ገበያ ተኮር ምርቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም የተናገሩት ዶክተር ነጋሽ የክልሉ መንግስት ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ዕድገት ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

‎የግል ባለሀብቶች ከመደበኛው ኢንቨስትንነት ስራ ጎንለጎን የአካባቢውን ማህበረሰብ በተለያዩ ዘርፎች ማገልገል እንዳለባቸውም ርዕሰመስዳደድሩ ገልጸዋል።

‎የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን በማስፋት ክልሉን ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የመንግስት ትኩረት መስኮችን በመለየትና ከግሉ ባለሀብት የሚነሱ አቅጣጫዎች መሠረት በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በቅንጅት ለመፍታት ያለመ መሆኑንም አቶ ታሪኩ ገልጸዋል።

‎የፎረሙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በተደራጀ መንገድ ለመፍታትና የክልሉን የኢንቨስትመንት አቅም ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

‎#SWMN