ማሻ፤ የካቲት 20/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከባለሃብቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ክልላዊ የኢንቨስትመንት ፎረም በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።
መድረኩ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በተደራጀ መንገድ ለመፍታትና የክልሉን የኢንቨስትመንት ፍሰት ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
የፎረሙን ማጠቃለያ መድረክ የመሩት የክልሉ ርዕሰመስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ያደጉ ሀገራት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ያስመዘገቡት በግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ታግዘው መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንት መሠረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት በትብብር መስራት እንደሚገባ የገለጹት ርዕሰመስተዳድሩ ከአገልግሎት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የማያዳግም እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ተናግረዋል።
የግሉ ዘርፍ የፈጠረውን አቅም በመጠቀም ገበያ ተኮር ምርቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም የተናገሩት ዶክተር ነጋሽ የክልሉ መንግስት ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ዕድገት ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
የግል ባለሀብቶች ከመደበኛው ኢንቨስትንነት ስራ ጎንለጎን የአካባቢውን ማህበረሰብ በተለያዩ ዘርፎች ማገልገል እንዳለባቸውም ርዕሰመስዳደድሩ ገልጸዋል።
የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን በማስፋት ክልሉን ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የመንግስት ትኩረት መስኮችን በመለየትና ከግሉ ባለሀብት የሚነሱ አቅጣጫዎች መሠረት በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በቅንጅት ለመፍታት ያለመ መሆኑንም አቶ ታሪኩ ገልጸዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በተደራጀ መንገድ ለመፍታትና የክልሉን የኢንቨስትመንት አቅም ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።
#SWMN
ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ዕድገት ማነቆ የሚሆኑ ችግሮች ተለይተው በዘላቂነት መፈታት አለባቸው፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
More Stories
የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት ዳግም ያረጋገጡ አዲስ የአርኪዮሎጂ ግኝቶች…
በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የበልግ ተጠቃሚ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ዝናብ ያገኛሉ ተባለ
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ ከኢራን ጋር ድርድር ሊኖር እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ