February 19, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኢትዮጵያዊ ርዕይን ለማሻገር የትናንቱን የመስዋዕትነት ችቦ በሥራ ወዳድነት ማስቀጠል ይገባል

ማሻ፤ የካቲት 12/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የዘመናችን የዕውቀትና የሥራ ዓርበኞች ከፍ ያለውን ኢትዮጵያዊ ርዕይን ለማሻገር የትናንቱን የመስዋዕትነት ችቦ በሥራ ወዳድነት አስቀጥሉት ሲሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ አስገነዘቡ።

ፕሬዚዳንት ታዬ ለ89ኛው የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም ይህ መታሰቢያ ኢትዮጵያን ማፍቀርና መውደድ፤ ለኢትዮጵያ ራስን ፈጽሞ መስጠት ምንጊዜም የማይጠፋ የሐሳብ እቶን እና የማይበርድ የመንፈስ ሙቀት መሆኑን ያስመሰከርንበት ነው ብለዋል።

ራስን ለታላቅ ሀገራዊ ርዕይ አሳልፎ መስጠቱ በኢትዮጵያ የነበረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ለአንድነቷና ለዕድገቷ በሚተጉ ዜጎቿ ዛሬም ሲገለጥ የምናየው ነገም በኢትዮጵያዊነት ፍቅር ፀንቶ የሚኖር ህያው ኃይል እና የማያቋርጥ ጥሪ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የዘመናችን የዕውቀትና የሥራ ዓርበኞች ከፍ ያለውን ኢትዮጵያዊ ርዕይና ተስፋችንን ለማሻገር የትናንቱን የመስዋዕትነት ችቦ በጥበብ ፈላጊነት እና በሥራ ወዳድነት አስቀጥሉት ሲሉም አስገንዝበዋል በመልዕክታቸው።(ኢዜአ)