ማሻ፤ የካቲት 9/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በሰሜናዊ ናይጀሪያ ሞተር ሳይክል በመጠቀም በተፈጸመው የታጣቂዎች ጥቃት 46 ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ጥቃቱ በሦስት የተለያዩ መንደሮች ውስጥ የተፈጸመ ሲሆን፥ ለህልፈት ከተዳረጉት በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውን የአልጀዚራ ዘገባ ያመላክታል።
በኒጀር ግዛት የተፈጸመው ጥቃት ከአሸባሪው አይ ኤስ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ እና ሰዎችን በማገት ገንዘብ የሚጠይቁ ታጣቂዎች አማካኝነት ሳይፈጸም እንደማይቀርም ዘገባው አመላክቷል።
በጥቃቱ በርካታ መኖሪያ ቤቶችም በእሳት የተቃጠሉ ሲሆን፥ እስካሁን ያልተለየ አስከሬን መኖሩንም ባለስልጣናቱ ገልጸዋል።
በሰሜናዊ ናይጀሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየጨመሩ መጥተዋል።
#አራዳ ኤፍ ኤም
More Stories
ኢራን እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት የተኩስ አቁም ስምምነቱን ትርጉም አልባ ያደርገዋል አለች
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ገመገሙ