ማሻ፤ የካቲት 2/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ መንግስት በጀት ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን የባቹማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የኮሌጁ ግንባታ በ2011 ዓ/ም በቀድሞው የደቡብ ክልል ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች የተቋረጠ ሲሆን፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት በ2017 ዓ/ም ውሉን እንደገና በማሳደስ ግንባታውን በድጋሚ በማስጀመር ቅርብ ድጋፍና ክትትል በማጠናከር በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታውን አጠናቅቆ ለምረቃ አብቅቷል።
በመርሐግብሩ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ፣ የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ሲል የዘገበው የክልሉ መ/ኮ ነው
More Stories
ውስጣዊ ሰላምን ማፅናት፦ ወቅቱ የሚጠይቀው አርበኝነት
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በካፋ ዞን የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ
የዲዚ ብሔረሰብ ማህበራዊ ድልብ ሀብቶችን ለክልላዊ አንድነትና ልማት ማዋል ይገባል፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)