ማሻ፣ ታህሳስ 15/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ትውልድን በስነ – ምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ አዲስ ለተመደቡና እና ለነባር የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክተሮች ፣ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በሚዛን ቴፒ ዩንቨርስቲ ቴፒ ግቢ በመስጠት ላይ ይገኛል ።
ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በማደናቀፍ በህዝብ እና በመንግሥት መካከል ያለውን ግኑኝነት በማሻከር በሀገር ዕድገት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን የሚያስከትሉ መሆናቸው ይታወቃል።
የክልሉ ስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ በወቅቱ እንደገለፁት ሀብትን በተገቢው ማሳወቅና ማስመዝገብ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከል ባሻገር ግልፀኝነትን እንዲፈጠር ያለው ፍይዳ የጎላ በመሆኑ በትኩረት ሊሠራበት እንደሚገባ ነው የገለፁት ።
በክልሉ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስነ-ምግባር ትምህርት ሥርፀት ዳይሬክተር አቶ በፍቃዱ ዘለቀ የሀብት ምዝገባ እና ማሳወቅ ዓላማዎችን ጨምሮ በአዋጆችና ደንበኞች ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ሲሰጡ ሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የሚረዳ ስልት ነው ብለዋል ።
የአሰራር ሥርዓት ጥናት መሠረታዊ ሀሳቦችንና ሂደትን መከተል ሌላኛው ሙስናን ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በክልሉ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስነምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይረክተሬት ወ/ሮ ጥሩእሸት ደቦጭ ናቸው ።
ስልጠናው የኮሚሽኑ አዋጆችና መመሪያ ፣ ሙስናና የጥቅም ግጭት ፣ሙስናን መከላከል ፣በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ማካሄድ እንዲሁም የአሰራር ጥናት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ።
More Stories
ፕሬዚዳንት ታዬ ለፈረንጆች የገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ጃፓን የዓለማችን ትልቁን የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዳግም ስራ ልታስጀምር ነው
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን የቡና ልማት ሊያሳድግ የሚችለው ግዙፍ ፕሮጀክት