ዶ/ር ደረጄ የወባ መከላከያ ክትባትና የአልጋ አጎበር ስርጭትን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ቱርሚ ከተማ በመገኘት በይፋ አስጀምረዋል።
በወቅቱም በሽታን በ2030 ለማጥፋት እየተደረገ ባለው ርብርብ የጸረ ወባ ክትባት ዘመቻው ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ገልጸው÷ ክትባቱ የወባ ስርጭት ባለባቸው 58 ወረዳዎች እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
ክትባቱ በዓለም ጤና ድርጅት ውጤታማነቱ የተረጋገጠና አስተማማኝ መሆኑን አንስተው፥ ወላጆችና አሳዳጊዎች ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን በማስከተብ ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የአልጋ አጎበሮች የወባ ጫና ላሉባቸው አካባቢዎች እንደሚሰራጩ መናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች