ዶ/ር ደረጄ የወባ መከላከያ ክትባትና የአልጋ አጎበር ስርጭትን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ቱርሚ ከተማ በመገኘት በይፋ አስጀምረዋል።
በወቅቱም በሽታን በ2030 ለማጥፋት እየተደረገ ባለው ርብርብ የጸረ ወባ ክትባት ዘመቻው ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ገልጸው÷ ክትባቱ የወባ ስርጭት ባለባቸው 58 ወረዳዎች እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
ክትባቱ በዓለም ጤና ድርጅት ውጤታማነቱ የተረጋገጠና አስተማማኝ መሆኑን አንስተው፥ ወላጆችና አሳዳጊዎች ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን በማስከተብ ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የአልጋ አጎበሮች የወባ ጫና ላሉባቸው አካባቢዎች እንደሚሰራጩ መናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በጋራ ስንቆም ከተራራ የገዘፍን ከብረት የጠነከርን ስለመሆናችን ህያው ምስክር ነዉ :-ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾ