ማሻ ፣ የሰኔ 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ፌቨን ጉርጁ ትባላለች በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ በ2017 ዓ.ም ከአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች ውስጥ 4 ነጥብ በማምጣት በባሕርዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሳይበር ደህንነት የጥናት መስክ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃለች።
ፌቨን ጉርጁ ከ53 ኮርሶች 42ቱን A+ በማምጣትም የዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችላለች፡፡
ፌቨን ዩኒቨርሰቲ ከመግባቷ በፊት በነበሩ የትምህርት ደረጃዎች ጥሩ ውጤት እያመጣች እዚህ እንደደረሰች ለኢቢሲ ተናግራለች።
ዩኒቨርስቲ ከገባሁ በኋላም ጥሩ ውጤት አምጥቼ መመረቅ ህልሜ ነበር፤ አሳክቸዋለሁም ትላለች።
ለውጤታማነቴ ከፈጣሪ በታች የቤተሰቦቼ፣ የመምህራኖች ጠንካራ ድጋፍ እና ያደረጉት ጥረት ለውጤት አብቅቶኛል ብላለች።
ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት እውቀት ያላቸው የሰው ሀይል ያስፈልጋታል፤ በዚህም በተመረኩበት መስክ አገለግላለሁ ስትል የወደፊት እቅዷንም ተናግራለች።
ኢቢሲ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።