ማሻ ፣ የግንቦት 16፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች ዕቅድ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት እየተገመገመ ይገኛል።
በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት ያለዉን ዉስን በጀት በካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ በፍትሃዊነት፣በአዋጭነትና ከአስፈላጊነት አኳያ አይቶ በጀት መመደብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ያለዉን ዉስን ሃብት አስቀድሞ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለመጨረስ እንዲሁም ዉጤታማ ስራ ለመስራት የካፒታል ፕሮጀክቶችን የበጀት ፍላጎት መገምገም እንዳስፈለገ ጠቅሰዋል።
ነባር የካፒታል ፕሮጀክቶች እና አዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክት በጀት ጥያቄ ያላቸዉ ቢሮዎች ዕቅዳቸዉን እያቀረቡ ይገኛሉ።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል – የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
የ2017 የፈተና አስተዳደር ስረዓት ዉጤታማ ለማድረግ በየደረጃዉ ያሉ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባቸዋል ተባለ።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች ነው።