በአሜሪካ 64 ሰዎችን ይዞ ሲበር የነበረ የመንገደኞች አውሮፕላን በሮናልድ ሬገን አየር ማረፊያ ለማረፍ ሲቃረብ ከጦር ሄሊኮብተር ጋር ተጋጭቶ መውደቁ ተገልጿ።
ቦምባርዲየር CRJ-700 የተሰኘው የሀገር ውስጥ የበረራ አውሮፕላን 60 ተሳፋሪዎችን እና አራት የበረራ አባላትን አሳፍሮ እንደነበር ነው የተገለፀው።
በአደጋው የመንገደኞች አውሮፕላኑ በፖቶማክ ወንዝ ውስጥ በመግባቱ የህይወት አድን ጀልባዎች እና ጠላቂዎች ፍለጋ ላይ መሆናቸው ተነግሯል።
አደጋ የደረሰበት የመንገደኞች አውሮፕላኑ መነሻውን ከዊቺታ ካንሳስ አድርጎ መዳረሻውን ወደ ዋሽንግተን እንደነበር ተገልጿል።
ከአውሮፕላኑ ጋር የተጋጨው የጦር ሄሌኮብተር ደግሞ ሶስት የአሜሪካ ጦር ወታደሮችን ይዞ እንደነበር የመከላከያ ባለስልጣን ተናግረዋል።
ስለአደጋው ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ፕሬዝዳንቱ በሰጡት መግለጫ “በመጀመሪያ ምላሽ ሰጪዎቻችን እየሰሩት ላለው አስደናቂ ስራ እናመሰግናለን፣ ሁኔታውን እየተከታተልን ሲሆን ተጨማሪ ዝርዝሮችን እንሰጣለን” ሲሉ ተናግረዋል።
የአደጋውን ምክንያት እና ዝርዝር ጉዳዮች አስመልክቶ የአሜሪካ ፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር ምርመራ እያካሄድኩ ነው ብሏል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።#Ebc
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች