በየማሻ ከተማ አስተዳደር በመልካም አስተዳደርና አጠቃላይ የልማት ሥራዎች ዙሪያ የህዝብ አቀፍ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ ማካሄድ ጀምረዋል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የማሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሠራዊት አየነው እንደገለጹት እንድህ ዓይነት መድረክ ለቀጣይ ስራዎች አጋጅ በመሆኑ እስከአሁን ድረስ የተከናወኑ ስራን በጋራ በመገምገም ለቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል።
የከተማን ዕድገት ለማፋጠን የህዝቡ ድጋፍ በእጅግ ስለሚያስፈልግ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከር በጉለቶች በታዩት ላይ የጋራ ርብርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አቶ ሰራዊት ተናግረዋል።
የማሻ ከተማ ማህበረሰብ ለከተማ ዕድገት በሁሉም ዘርፍ ድጋፍ ከማድረግ ወደ ኃላ ብሎ የማያውቅ ህዝብ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሠራዊት አሁንም ቢሆን የተለመደውን ትብብር በገንዘብ በጉልበትና በሐሳብ ከመንግስት ጎን እንድቆሙ ጠይቀዋል።
በቀጣይ ተግባራቶቻችን ላይ የህዝቡ ዕገዛ በእጅጉ ስለሚያስፈልግ ሁሉም የመድረጉ ተሳታፊዎች የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ከከተማ አስተዳደሩ ጎን እንድቆም ከንቲባው ጥሪውን አስተላልፏል።
ዘጋቢ ካሳሁን ደንበሎ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።