ማሻ፣ ጥር 6፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ)”ቢስት ባር “የመደመር እሳቤ በተግባር የሚገለጽበት በዓል ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርእሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)ተናገሩ፡፡
የቤንች ብሔር ዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል “ቢስት ባር” ማጠቃለያ መርሐ ግብር በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።
በበዓሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርእሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋነሽ ኬሌሮ፣ የፌደራልና የክልል የስራ ሀላፊዎች፣ የቤንች ብሔር የጎሳ መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎችም ታድመዋል።
ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ በቢስት ባር በዓል የብሔሩ አባላት ተሰብስበው በአብሮነት የሚያሳልፉትና መጪውን አዲስ የመደመር አስተሳሰብ በተጨባጭ የሚገለጽበት ነው ብለዋል።
ይህ ድንቅ ባህል ተጠንቶና ተሰንዶ ለትውልዱ ሊተላለፍ ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ፥ የብሔሩ ምሁራን ማህበረሰቡ ያዳበረውን ቱባ የባህል እሴት ለሰላምና ለዕድገት እንዲውል በማድረግ ሁሉም የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን÷ የለውጡ መንግስት ለባህል በሰጠው ትኩረት በርካታ ቱሪስቶች አካባቢው እየጎበኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ቢስት ባር ለበኩር ቅድሚያ የሚሰጥበት፣ መተሳሰብ ፣ መደማመጥ ያለበት ድንቅ በዓል ነው ያሉት አስተዳዳሪው ይህንን በዓል ለቀጣይ ትውልድ ጠብቆ የማቆየት ሃላፊነት አለብን ነው ያሉት፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረፋ(ዒድ አል አድሃ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም የተገቡ ቃሎች አንድ በአንድ እየተተገበሩ ናቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ሸለሙ