ከተማ አስተዳደሩ ከማሻ 30 አስከ ማድያ ደረስ ካሉት የከተማ ነዋሪዎች ጋር በከተማው አሰፓልት መንገድ ስራ ዙርያ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።
በመድረኩም ላይ የተገኙት የማሻ ከተማ ከንቲባ አቶ ሠራዊት አየነው እንደገለፁት መንግሥት የከተሞችን እድገት ለማሳለጥ ከፍተኛ ጥሬት እያደረገ ባለበት ወቅት የማሻ ከተማን እንደ ሌሎቹ ከተሞች ለማሳደግ ህብረተሰቡ ከመንግሥት ጎን ሆኖ እንድደግፍ ገልፀዋል።
በማሻ ከተማ የሚጀምረውን አስፓልት መንገድ ለከተማው እድገት ይበልጥ እንድሳለጥ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ያነሱት አቶ ሠራዊት ለዚህም ስራ ስኬት የከተማ ነዋሪዎች ድርሻ የጎላ ልሆን ይገባል ብለዋል።
ይህ ስራ ውጤታማ እንድሆን ከከተማ ነዋሪዎችና በበየደረጃው ከሚገኙ አካላት ጋር በመተማመን ስራ እንድጀመር መደረጉን ተናግረዋል።
የማሻ ከተማ የመንግሥት ዋና ተጠር አቶ መልካሙ እንዳሻው በበኩላቸው ያለህብረተሰብ ተሳትፎ የከተማውን እድገት ማረጋገጥ እንደማይቻል ገልፀው ለዝህም ተቀናጀቶ መስራት ቀዳም ተግባር ልሆን ይገባል ብለዋል ።
የውይይቱ ተሳታፍዎች በበኩላቸው መመሪያውና ደንቡ በሚለው መሠረት የንብረታቸው ካሣ እንድከፈልላቸው በመጠየቅ ለከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ገልፀዋል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች