ማሻ፡ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ወቅቱን ሊመጥን የሚችልና በየጊዜው እያደገ በሚሄደው የዘርፉ ውድድር በብቃት መሳተፍ የሚችል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስርኣት ግንባታ ጠንካራ ቅንጅትና መናበብን ይጠይቃል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ተናግረዋል።
ዶ/ር ዲላሞ ከክልሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አመራሮች ጋር በዘርፉ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ በሆሳዕና ከተማ እየተወያዩ ሲሆን በዚሁ ወቅት እንዳሉት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ወቅቱን የሚመጥኑ እንዲሆኑ ዘላቂና ጠንካራ የአመራር ቅንጅትን ይጠይቃሉ።
ከዚህ መነሻ እውነትን መሰረት ያደረጉ መረጃዎችን ለህዝብ በወቅቱ ተደራሽ ማድረግና በህብረተሰቡ ውስጥ የመጣውን አዎንታዊ ለውጥ በየጊዜው ለመገምገም የሚያስችል የሚዲያ አመራር ስርዓት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል።
የክልሉ የህዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሰብስቤ ተካ ባቀረቡት የውይይት ሰነድ በበኩላቸው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የመረጃ የበላይነትን ሊያረጋግጡ የሚችሉ፣ ገዢ ትርክትን የሚያሰርጹና ሀገራዊ የለውጥ ራዕይን መሰረት ያደረጉ መሆን አለባቸው ብለዋል።
በውይይቱ የመንግስትና የፓርቲ የሚዲያ ዘርፍ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ሲሆን የክልሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን የትኩረት አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ምንጭ ደሬቴድ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች