ማሻ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ ኑክሌር፣ ራዲዬሽንና ኬሚካል ጥበቃ ኃይል ዋና ኃላፊ ሌተናንት ጀነራል ኢጎር ኪሪሎቭ እና እረዳታቸው በተጠመደ ፈንጂ ምክንያት ሞስኮ ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
ኃላፊው እና እረዳታቸው ሕይወታቸው ያለፈው ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ በስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ መሆኑን የሀገሪቱ መርማሪ ኮሚቴ አስታውቋል።
300 ግራም የሚመዝነው ፈንጂ በርቀት መቆጣጠሪያ አማካኝነት መፈንዳቱን ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ሌተናንት ጄነራሉ የተከለከለ ኬሚካል በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቅደዋል በሚል ዩክሬን ትናንት መክሰሷ ይታወሳል፡
More Stories
በቀጣዮቹ ቀናት በበርካታ አካባቢዎች የክረምቱ ዝናብ ተጠናክሮ ይቀጥላል
በአዕምሮ የበለጸገ ትውልድ እንዲፈጠር የምግብ -ስርዓትና ስርዓተ – ምግብ ትግበራዎችን በቅንጅት መምራት እንደሚገባ ተገለጸ
267ኛው የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ መመረጡን አስመልክቶ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የተሰበሰቡ ምዕመናን ደስታቸውን ሲገልፁ