ማሻ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ ኑክሌር፣ ራዲዬሽንና ኬሚካል ጥበቃ ኃይል ዋና ኃላፊ ሌተናንት ጀነራል ኢጎር ኪሪሎቭ እና እረዳታቸው በተጠመደ ፈንጂ ምክንያት ሞስኮ ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
ኃላፊው እና እረዳታቸው ሕይወታቸው ያለፈው ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ በስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ መሆኑን የሀገሪቱ መርማሪ ኮሚቴ አስታውቋል።
300 ግራም የሚመዝነው ፈንጂ በርቀት መቆጣጠሪያ አማካኝነት መፈንዳቱን ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ሌተናንት ጄነራሉ የተከለከለ ኬሚካል በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቅደዋል በሚል ዩክሬን ትናንት መክሰሷ ይታወሳል፡
More Stories
የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ በመምህር ዳኪቶ ጋወቶ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ።
ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ
መልካም አብነቶች በማስፋት ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ እናፋጥናለን – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)