የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የባህልና ቱሪዝም ኤግዚቢሽን እና ፌስቲቫል በአርባ ምንጭ ከተማ በይፋ ከፍተዋል። 19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ዋዜማ በአርባ ምንጭ ከተማ በተለያዩ ዝግጅት እየተከበረ ይገኛል። የበዓሉ አካል የሆነው 32 ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የየራሳቸው ቅርስ እና ባህላዊ ቁሶችን የሚያስጎበኙበት ባህላዊ ፌስቲቫል ዛሬ ተጀምሯል፡፡ 19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በተለያዩ ስያሜዎች የሚከበር ሲሆን ህዳር 26 የደቡብ ኢትዮጵያ ቀን በመባል ይከበራል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።