
ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራር የብቃት ስልጠና ሊሰጥ ነው
በመጪው ክረምት ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራሮች የብቃት ስልጠና እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል ።
ስልጠናው የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍና የመምህራን ብቃትን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን÷ በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ይሰጣል ነው የተባለው።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን እና የትምህርት አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ(ዶ/ር) መምህራኑ የሚሰለጥኑት በሚያስተምሩት ትምህርትና በማስተማሪያ ዘዴዎች መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል ።
ለ42 ሺህ መምህራን 120 ሰዓት፤ ለ8 ሺህ የትምህርት አመራሮች ደግሞ የ60 ሰዓት ስልጠና እንደሚሰጣቸው የተገለፀ ሲሆን ÷ሲያጠናቅቁም ፈተና እንደሚወስዱ ነው ስራ አስፈጻሚው የተናገሩት፡፡
ስልጠናው በመምህራንና የትምህርት አመራሩ ላይ ያለውን የማስተማር ዘዴዎችና የእውቀት ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ ታምኖበታል፡፡
More Stories
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን
ምክር ቤቶች የህዝቡ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት እንድረጋጥ ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ማጠናከር እንደምያስፈልግ ተጠቆመ ።
ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ እያከናወነች ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው