6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ- ሥርዓት ነገ ይካሄዳል። በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ1 ዓመት ስራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ አስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ድንጋጌ መሰረት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት በተገኙበት ነገ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ለሁለቱ የፌደራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ስራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌደራል መንግስቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚገኙ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
EBC
More Stories
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት (ሰኔ 9) በኢቢሲ ሁሉም አማራጮች ከምሽቱ 2:30 ላይ ይከታተሉ።
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን