የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር አስተዋጽዖ ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ፡፡የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ በድምቀት ተከብሯል፡፡ይህን ተከትሎም በዓሉን እሴቱን ጠብቆ በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን ማመስገናቸውን የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡በነገው ዕለትም በቢሾፍቱ ከተማ ‘ሆረ ሀርሰዲ’ እንደሚከበር ገልጸው÷ በዓሉ ዕሴቱን በጠበቀ ሁኔታ በድምቀት እንዲከበር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅረበዋል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።