የሸካቾ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ ባሮ” በክልሉ ከሚገኙ ቱባ ባህሎች አንዱ መሆኑንና የህዝቦችን ትስስር ፣አንድነት፣ ህብረብሔራዊነትን በማጎልበት ረገድ ባህል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የክልሉ ባህል ቱርዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ተናገሩ ።ባህልን ማልማት፣መንከባከብ ፣መጠበቅ፣ የህዝቦች ትልቅ የማዕዘን ድንጋይ፣መነሻ ታሪካቸውን የሚያዩበት መነጽር፣ ዘላቂ ልማትና ሰላምን ለማረጋገጥ የሚያስችል ወሳኝ እሴት ነው ሲሉም የቢሮው ኃላፍ አክለዋል።የባህልና የቋንቋ መብቶች ተጠብቀው የሚካሄዱት ክዋኔዎች ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ስለሆነ ለትውልድ ማስተማርና ማስተላለፍ ያስፈልጋል ተብሏል።
የሸካቾ ዘመን መለወጫ/ማሽቃሮ/ በዓል በደማቅ ባህላዊና ታሪካዊ ስነስርዓቶች “በሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ ገጫ” በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ