በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (የተመድ) ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከኡጋንዳ እና ርዋንዳ አቻቸው ጋር ተወያይተዋል።አምባሳደር ታዬ ከኡጋንዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢሊቪየር ኑሁንጊሬሄ እና የርዋንዳ ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ጄጄ ኦዶንጎ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።ከርዋንዳው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄጄ ኦዶንጋ ጋር በነበራቸው ውይይት በናይል የውሃ ሃብት ፍትሃዊ አጠቃቀም ላይ ሁለቱ ሀገራት ስላላቸው የጋራ አቋም ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።ከኡጋንዳው አቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይትም በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሰላም ሁኔታ ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በድህረ በሶማሊያ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ሰላም ማስከበር ተልዕኮ (አትሚስ) መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች እና አጠቃላይ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በሶማሊያ ሰራዊት አሰማርተው የነበሩ በመሆናቸው ድህረ አትሚስ ሽብርተኝነትን በመዋጋት የተመዘገበው ውጤት ወደኋላ በማይመልስ መልኩ መፈጸም እንዳለበት መክረዋል።በጥቅምት ወር አጋማሽ ላይ ኡጋንዳ የምታስተናግደው የናይል ጉባዔ የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ወደ ተግባር እንዲገባ የሚያስችሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሚሆን ያላቸውን እምነት አምባሳደር ታዬ ገልጸዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።