ኢትዮ ቴሌኮም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ10 ሚሊዮን ብር እንደተቋም እንዲሁም ከደንበኞች ያሰባሰበውን 1.35 ሚሊዮን ብር በድምሩ ከ11.35 ሚሊዮን ብር በላይ አስረከበ፡፡ኩባንያው በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋው የተጎዱትን ወገኖች መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት ለማገዝ የሚያስችለውን የብር ድጋፍ ከደንበኞች፣ በቴሌብር እና በ8090 አጭር ቁጥር ያሰባሰበውን ድጋፍ ጨምሮ ለጎፋ ዞን የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ምላሽ ፈንድ በዛሬ ዕለት አስረክቧል፡፡የኩባንያው ከፍተኛ አመራር ተወካዮች በጎፋ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝተው በዜጎች ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን የገለጹ ሲሆን በዚህም ወቅት ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም እያደረገ የሚገኘውን ሁለገብ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፣ ዜጎችን የማቋቋሙ ስራ እስኪጠናቀቅ ድረስ ማህበረሰቡ ድጋፍ ለማሰባሰብ የተከፈቱ የቴሌብር እና የአጭር ቁጥር 8091 በመጠቀም አቅም የፈቀደውን ድጋፍ ማድረጉን
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።